አቡነ ማርቆስ VS ምሥራቅ ጎጃም ምእመናን
አቡነ ማርቆስ VS ምሥራቅ ጎጃም አስተዳድር ጽ/ቤት
አቡነ ማርቆስ VS ሰንበት ትምህርት ቤት
አቡነ ማርቆስ VS ማኅበረ ቅዱሳን
ዛሬ ጥቅምት 3/2010 ዓ.ም ነው፡፡
==============================
·
ጸሎተ ምሕላው እንደቀጠለ ነው፡፡
·
አቡነ ማርቆስ የምሥራቅ ጎጃም
ዞን አስተዳድር ጽ/ቤትን የተሳደቡበት በድብቅ የተቀረጸ መረጃ ይፋ ሆኗል ወደፊት በትእግሥት ጠብቁኝ፡፡
·
በደብረ ማርቆስ ከተማ የሚገኘው
የመልእልተ አድባር ቅዱስ ማርቆስ ሰንበት ትምህርት ቤት በአባ ወልደ ትንሣኤ እንዲዳከም አድርገው የተኳቸውን የሰንበት ትምህርት
ቤት ሥራ አስፈጻሚዎችን ከነ ሙሉ መረጃቸው ደርሶኛል ይህንንም በትእግሥት ጠብቁኝ፡፡
ብጹእ አቡነ ማርቆስ በምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት
ከመጡበት 2004 ዓ.ም ጀምሮ ከምእመናን ዘንድ ከፍተኛ ተቃውሞ ሲገጥማቸው እስካሁን ድረስ አሉ፡፡ ይህን ሀገረ ስብከት ከተረከቡበት
ጀምሮ ምእመናን ተቃውሟቸውን ለቅዱስ ሲኖዶስ ሲያሰሙ ቆይተዋል አሁንም ድረስ በማሰማት ላይ ናቸው፡፡ ለምሳሌ በ2005 የነበረውን
ተቃውሞ የፊርማ ማሰባሰቢያ ደብዳቤ እንዲህ ይመለከታል፡፡
==========================================================================================
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ
አሐዱ አምላክ አሜን!
ቀን፡- ኅዳር30/2005 ዓ.ም
ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ
ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ጽ/ቤት
አዲስ አበባ
ብፁዓን አበው ሊቃነ ጳጳሳት፣
ከሁሉም በፊት የሀገረ ስብከቱን ምእመናን አቤቱታ ለመስማት በመፍቀዳችሁ በእግዚአብሔር ስም
እያመሰገንን እኛ በሀገረ ስብከቱ በተለይም በደብረ ማርቆስ ከተማና አካባቢው የምንኖር የቤተክርስቲያን ልጆች በሀገረ ስብከቱ
የተከሰቱትንና እየተከሰቱ ያሉትን ሃይማኖታዊና አስተዳደራዊ ችግሮች ለመፍታት ከብፁዕነታቸው ጋር የመንግስት ከፍተኛ የአመራር
አካላትንም በመጨመር ተደጋጋሚ ውይይት ለማድረግ የሞከርን ቢሆንም ብፁዕነታቸው በሚያሳዩት አባታዊ ያልሆኑ ንግግሮች ውጤታማ
ሊሆን አልቻለም፡፡ እኛም የቤተክርስቲያኒቱ ልጆች ተሰባስበን በመወያየት የቤተክርስቲያኒቱን እሴት የሚያንኳስሱ
ክንዋኔዎች፤አሠራሮችና ሁኔታዎች ከዕለት ዕለት እየበዙ በመምጣታቸው ጉዳዩን ለቤተክርስቲያኒቱ የበላይ አካል ለቅዱስ ሲኖድስ
ሰላማዊና ተቋማዊ መዋቅሩን በጠበቀ መልኩ ይኸው ዛሬ ለማቅረብ ተገደናል፡፡
ምክንያቱም፡-
í) በሀገረ ስብከታችን እየተከሰቱ ያሉ አስተዳደራዊና ሃይማኖታዊ ችግሮችን ከምንጩ ለማስረዳት፤
î) አሁን የተከሰቱትና እየተከሰቱ ያሉት ሃይማኖታዊና አስተዳደራዊ ችግሮች ምንም መፍትሔ ሳይበጅላቸው
በዚህ አካሄድ ከቀጠሉ ለሀገረ ስብከታችን እና ለመላ ቤተክርስቲያናችን ውስብስብና ዘርፈ ብዙ ጉዳቶችን ሊያስከትል የሚችል
በመሆኑ ከወዲሁ መፍትሔ እንዲፈለግበት፤
ï) ሀገረ ስብከታችን ልዩ ትኩረት የሚያስፈልገው “ከቅባት” ጋር የተገናኙ ችግሮች ያሉበት በመሆኑ
ብፁዐን ሊቃነ ጳጳሳት አባቶቻችንና መላ የቤተክርስቲያኒቱ ልጆች ልዩ ትኩረት እንዲሠጡት ለማስገንዘብ ሲሆን ብፁዕነታቸው አቡነ
ማርቆስም በተደጋጋሚ ራሳቸውን ከሁሉም የተለዩ ፣የማይገኙ ፣ የማይተኩ ፣ እሳቸው ያሉትን የማይቀበል ያልዳነና ያልገባው መሆኑን
በመግለጽ ካህናቱን በመሳደብ፣ ምእመኑን ወንጌል ያልገባው በደብተራ የተተበተበ እና ሌሎች የንቀት፣ የስድብ እና የእርግማን
ንግግሮችን በመናገር የበደሉን በመሆኑ ለችግሮች መፍትሔ ለማፈላለግ እንጂ አቤቱታችን ከጭፍን ጥላቻና ነቀፌታ የነፃ ፍጹም
ሃይማኖታዊና አስተዳደራዊ መፍትሄን በመሻት ነው፡፡
íኛ.
አስተዳደራዊ ችግሮች
ብፁዕነታቸው አቡነ ማርቆስ ወደ ምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት እንደመጡ ብዙ ጉዳዮችን በትችት
ሕዝቡንም በንቀት የተመለከቱ ሲሆን በመጡ በ3ኛ ወራቸው ጀምረው፡-
í) ከ41 በላይ ሹም ሽርና እገዳ
ያካሄዱ ሲሆን አብዛኛዎቹ ሹም ሽሮችና እገዳዎች ሕገ ቤተክርስቲያንን /ቃለ አዋዲውን/ ያልተከተሉ፤ተቋማዊ መዋቅሩን የጣሱ
ይገኙባቸዋል፡፡
î) ቅድስት ቤተክርስቲያን በቅዱስ ሲኖዶስ ፈቃድ በቃለ ዓዋዲው መሠረት የተቋቋሙትን ሰ/ት/ቤቶችን “ወንበዴዎች፤ሌቦችና አሸባሪዎች” በማለት በሕዝብ ፊት ተሳድበው
ለሰዳቢ ሠጥተዋል፡፡
ï በንጹሐን ምእመናን ላይ ሰብአዊ ክብርንና ነፃነትን የሚጋፋ የስድብ፤ንቀትና እርግማን
አካሄደዋል፡፡
ð ) ብፁዕነታቸው ከሦስት በላይ መኖሪያ ቤቶች ያሏቸው ሲሆን ከእነዚህም መካከል ተወልደው ባደጉበት፣
በተማሩበትና ባስተማሩበት ጉንደወይን ከተማ /በ2004 ዓ.ም የተገዛ/ እና አዲስ አበባ / በ2000 ዓ.ም የተገዛ/ ያላቸው
ሲሆን ከአዲስ አበባው መኖሪያ ቤት የግንባታ ውል ክፍያ ጋር በተያያዘ በብፁዕነታቸው በብፁዕ አቡነ ማርቆስ ላይ የተፈጸመው
ክስና እስራት በሀገረ ስብከታችን ያሉትን ምእመናንን አንገት ሰብሯል፤ አዋርዷል፡፡ በዚህም ወቅት በሀገረ ስብከታችን አስተዳደር ውስጥ በሂሳብ ሹም፣ ገንዘብ ያዥና መዝገብ ቤት
መካከል ሦስት ወራት ባልሞላ ጊዜ ውስጥ በአንድ ቀን የተደረጉ
ለውጦችና ሰዎቹ ለብፁዕነታቸው ካላቸው ዝምድናና አካሄድ አንጻር ነገሩን ለሀገረ ስብከቱ ምእመናን ከጥቂት ዓመታት በፊት በብፁዕነታቸው
አቡነ ዘካርያስ ከተፈጸመብን በደል አንጻር እንቅስቃሴውን እንቆቅልሽ አድርጎብናል፡፡
îኛ. ሃይማኖታዊ
ችግሮች
ብፁዕ አቡነ ማርቆስ ወደ ሀገረ ስብከታችን ከመጡበት ከኅዳር 2004 ዓ.ም ጀምሮ
በካህናት፤በዲያቆናትና በሌሎች የቤተክርስቲያኒቱ ምእመናን ዘንድ ያልተለመዱ፤እንግዳ ክንዋኔዎች እየተስተዋሉ ሲሆን ክንዋኔዎቹና
አሠራሮቹም ምእመናንን ግራ ያጋቡ፤ለመናፍቃንም በር የከፈቱና የሚከፍቱ ናቸው፡፡
ከእነዚህም መካከል ፡-
1 ) ብፁዕነታቸው አቡነ ማርቆስ ከመጡ ከሁለት ወራት በኋላ ጀምሮ የቅድስት ቤተክርስቲያናችን ቅዱሳን
አበው ለመናፍቃን መልስ የሰጡበትና ለአማኞች ያስተማሩበት ሃይማኖተ አበው መጽሐፍ ‹‹እኔ ልማታዊ ነኝ ጊዜውን በአግባቡ መጠቀም አለብን›› በሚል ተገቢ ያልሆነ ምክንያት ከቅዳሴ በኋላ
እንዳይነበብ ተደርጓል፡፡
)2 በአንዳንድ አድባራትና ገዳማት በውል በታወቀ ምክንያት የቅዳሴ ጸሎት ሰዓቱ ቢቀየርም በፍትሐ
ነገስት አንቀጽ 12 ላይ ‹‹ሕዝቡ ሳይሰበሰቡ የቅዳሴውን ጸሎት አይጀምሩ›› የሚለውን በመተው በሀገረ ስብከታችን ለብዙ ዘመናት
ምቹ ከሆነው ንጋት የ12፡00 ሰዓት የቅዳሴው ጸሎት ያለ ምንም ተጨባጭ ምክንያት ‹‹ሰዓቱን ለወንጌል መጠቀም አለብን›› በሚል ምክንያት ወደ 11፡00 ሰዓት እንዲሆን ተደርጓል፡፡በዚህም
እናቶች፤እህቶች፤ሕጻናትና አረጋዊያን ሌሊት 10፡00 ሰዓት ከቤታቸው እንዲወጡ በመገደዳቸው መቸገራቸውን፤መማረራቸውንና በቅዳሴ
ሰዓትም የምእመኑ ቁጥር መቀነሱን እንገልጻለን፡፡
3) በክብር ለቡራኬ በእጃችን በማድረግ እንቀበለው የነበረውን የቅዳሴ ጸበል
ያለ ምንም ምክንያትና ጥቅም ብፁዕነታቸው በጆግ በማደረግ በጅምላ ምዕመናንን መርጨት በማዘውተራቸው ምእመናንም ሲጠይቋቸው ‹‹እንግዲያውስ አረቄና ጠላ ልርጫችሁ?›› በማለት የተዘባበቱና
የመለሱ ሲሆን ነገና ከነገ ወዲያ ይህ አካሄድ ወደ ቅዱስ ቁርባኑ የማይሄድበት ምንም ተጨባጭ ምክንያት እንደማይኖር
እንገልጻለን፡፡
4) በቅዳሴ ጸሎት ጊዜ ታቦተ መንበሩን ለምእመናን ግልጥ ሆኖ እንዲታይ በማስገደድ (ካህናቱ ሥጋውና
ደሙን ሲፈትቱ እንዲታይ በማድረግ) በአካባቢው ሽማግሌዎች አበባል ‹‹የኢትዮጵያ
ሙሽራ ዛሬ ተገለጠ ክፉ ቀን መጣ›› እስኪባል ድረስ ብዙ ተቃውሞ ቢገጥማቸውም በቤተክርስቲያናችን ያልተለመደ የጸሎተ
ቅዳሴ ሥርዓት እንድንከተል እየተገደድን እንገኛለን፡፡
5) በቅድስት ቤተክርስቲያናችን የሥርዓት መጽሐፍት በሆነው በፍትሐ ነገስት መሠረት የጌታችን
የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ የጾሙን ወራት በሚታሰብበት በጾመ ኢየሱስ ወይም ዐቢይ ጾም በአርምሞ፤በጾምና በጸሎት፤በንስሐና ቅዱስ
ቁርባን፤በሱባኤ የጌታን ሕማማተ መስቀል እያሰቡ ማዘን፤ማልቀስ የሚገባ በመሆኑ ከበሮ የማይመታ የማይጨበጨብ ቢሆንም ብፁዕነታቸው
ይህንን ሥርዓት በመተው ምእመናን “አልለመድንም ከበሮ አንመታም
አናጨበጭብም” ቢሉም ‹‹እኔ ሊቀ ጳጳሱ ተቀምጬ፤እኔ ፊታችሁ
እያለሁ›› በማለት በደ/ማርቆስ ከተማ በሚገኘው ጽርሐ ጽዮን አብማ ማርያም ቤተክርስቲያን በተደረገ ጉባኤ ምእመኑ
ሳይፈልግ በማስገደድ ከበሮ አስመትተዋል፤ አስጨብጭበዋል፡፡
)6 ካህናት ምእመናንን በተለይም
የንስሐ ልጆቻቸውን በቅርብ መከታተል ይጠበቅባቸዋል፡፡ በዚህ መሰረት ካህናቱ በየንስሐ ልጆቻቸው ቤት በመዘዋወር ቡራኬ
ይሰጣሉ፡፡ ብፁዕነታቸው ግን የሀገረ ስብከቱን ካህናት ክብርን በሚነካ መልኩና በጸበሉ ፈዋሽነት አለማመንን በሚያሳይ አነጋገር ‹‹ውኃ ግድግዳ ላይ ከመርጨት በቀር ወንጌል የማያውቁ›› በማለት
ተሳድበዋል፡፡ ጸበል ውኃ ብቻ ነውን? ካህናቱስ አይባርኩትምን? እርሱስ መጻጉዕ የተፈወሰበት ወንጌል አይሆንም? ካህናቱስ ሌላ
አያውቁምን?
)7 በፍትሐ ነገስት አንቀጽ 14 ላይ በተገለጸው መሠረት ሴት
በወር አበባ(በወርኃ ጽጌ) ወቅትና አራስ ስትሆን ቤተክርስቲያን መግባትን የሚከለከል እንደሆነ ቢታወቅም ብፁዕነታቸው መግባት
እንደሚችሉ የፈቀዱ ሲሆን እርሳቸው በተገኙባቸው ጉባኤያት ላይ ‹‹እኔ
አባታችሁ እያዘዝሁ፣እኔ ፈቅጄ፣ እኔ የቤተክርስቲያኒቱ ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያው እያለሁ›› በማለት እንዲገቡ
በማስገደዳቸው የተወሰኑት እናቶችና እህቶች ትዛዛቸውን አክብረው ሲገቡ ቀሪዎቹ ለቤተክርስቲያን ክብር ሲሉ ወደ ቤታቸው ሲመለሱ
ማየት የተለመደ ትርኢት ሆኗል፡፡
)8 ብፁዕነታቸው ከላይ በተራ ቁጥር
ሁለት ከተጠቀሰው የቅዳሴ ጸሎት ሰዓቱን እንዲሻሻል ከማድረጋቸውም
በተጨማሪ በጸሎተ ቅዳሴ ጊዜ መውጣት እንጂ መግባት ይቻላል በማለት አባቶቻችንና ወላጆቻችን ያላስተማሩንን የማናውቀውን ሥርዓት
እንድንከተል እየተገደድን መሆናችንን እንገልጻለን፡፡
9) ብፁዕነታቸው ነገረ ቅዱሳንን
በተመለከተ ግራ የሚያጋባ አቋም ያላቸው ሲሆን የሀገረ ስብከቱ ሰባኪያነ ወንጌልን በመንበረ ጵጵስና ሰብስበው ‹‹ክርስቶስን ስበኩ እንጂ አቡሀይ እሙሀይ አትበሉ›› በማለት
ስለ ቅዱሳን ያላቸውን አመለካከት ተናግረዋል፡፡
በአጠቃላይ በሀገረ ስብከታችን
ብፅዕነታቸው ያደረሱብን ሃይማኖታዊና አስተዳደራዊ በደል እኝህ ብቻ ሳይሆኑ የተጠቀሱት ማስረጃ ማቅረብ የሚቻልባቸው ሲሆኑ በዚህ
ጹሑፍ ቢቀርቡ የቤተክርስቲያንና የአባቶቻችንን ክብር የሚያስደፈሩ በመሆናቸው ያላቀረብናቸው ሲሆን እኛ በምስራቅ ጎጃም ሀገረ
ስብከት የምንገኝ የቅድስት ቤተክርስቲያን ልጆች ከጥቂት ዓመታት በፊት በብፁዕነታቸው አቡነ ዘካርያስ የደረሰብን በደል ከልባችን
ሳይሽር ከኃሊናችን ሳይወጣ ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ለችግራችን መፍትሄ ለመፈለግና ምእመናንን ለመካስ ጥረት ቢያደርጉም ጥረታቸው
በብፁዕነታቸው መቀጠል ሲገባውና የደረሰብንን በደል መካስ ሲገባቸው ድጋሜ ዘርፈ ብዙና መሰረታዊ ሃይማኖታዊና አስተዳደራዊ
ችግሮች በመከሰታቸው ምክንያት ይህን ችግር ለብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አባቶቻችንና ለመላ የቤተክርስቲያኒቱ ልጆች ጉዳዩን ለመግለጽ
የተገደድን ሲሆን አስፈላጊውን ተቋማዊ መዋቅር ተከትለን ችግሩን ለመፍታት ጥረት ብናደርግም ባለመሳካቱና ምላሽ ባለማግኘታችን
መሆኑን እየገለጽን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት አባቶቻችን ይህን ጉዳይ በጥልቀትና በስፋት ተመልክተው መፍትሔ እንዲሰጡን ከዚህ ሸኝ ደብዳቤ
ጋር ባያያዝነው 116 ገጽ የድጋፍ ፊርማ እየገለጽን እኛ የሀገረ ስብከቱ ምእመናን በቅዱስ እግዚአብሔርና በቅዱሳኑ ስም እንጠይቃለን፡፡
“ቡራኬያችሁና ጸሎታችሁ አይለየን”
የምሥራቅ ጎጃም ሀገረ ስብከት ምእመናን ተወካዮች
ግልባጭ
- ለብፁዕ አቡነ ናትናኤል አቃቤ መንበረ ፓትርያርክ
- ለመንበረ
ፓትሪያሪክ ጠቅላይ ቤተክህነት ጽ/ቤት
- ለፓትሪያሪኩ
ልዩ ጽ/ቤት
- ለምሥራቅ
ጎጃም ዞን አስተዳደር ጽ/ቤት
- ለምሥራቅ
ጎጃም ዞን አስተዳደርና ጸጥታ ዘርፍ ጽ/ቤት
==========================================================================================
https://www.facebook.com/metshetewahido/videos/pcb.1932176840333243/1932176313666629/?type=3&theater
ይህ ከላይ በ2005 ዓ.ም የተጻፈው የተቃውሞ
ደብዳቤ ምንም ዓይነት ለውጥ አላመጣም፡፡ እንዲያውም ችግሮች ተባብሰው ነው የቀጠሉት፡፡ ነገር ግን ይህ ተቃውሞ በዚህ አላቆመም
በ2009 ዓ.ም ተቃውሞው በከፍተኛ ደረጃ ተቀጣጥሎ መውጣቱ ለሁሉም የታወቀ ጉዳይ ነው፡፡ የዚህን ተቃውሞ ፍሬ የምንመለከትበት ደግሞ
የጥቅምት ሲኖዶስን ነበር፡፡ ሆኖም ግን ይህንን ፍሬ ገና በአበባነቱ ለመቅጨት የሞከሩት ብጹእ አቡነ ማርቆስ በሀገረ ስብከቱ በሚገኙ
ምእመናን የተገነባውን ሁለገብ ህንጻ ህንጻው ሳይጠናቀቅ ለማስመረቅ ሞክረዋል፡፡ በዚህ የምረቃ ቀን መስከረም 27/2010 ዓ.ም
ቅዱስ ፓትርያርኩን ጨምረው የእኔ ያሏቸውንም ጳጳሳት አስከትለው በቦታው ተገኝተዋል፡፡ በነገራችን ላይ የአማራ ፖሊስ ኮሚሽን በእናንተ
ምክንያት የሰው ህይወት እንዲጠፋ አንሻምና በዚህ ምረቃ ቀን ፓትርያርኩ ባይገኙ ይመረጣል ብሎ ማሳሰቡን አውቀናል፡፡ የመጣው ይምጣ
ብለው የህዝቡን አቤቱታ ከመጤፍ ያልቆጠሩት አባ ማትያስ ግን በአጋዚ ጦር ተከበው እንደ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ታጅበው ደብረ ማርቆስ
መጥተዋል፡፡ ዋና ዓላማው አባ ማርቆስን በዚሁ ሀገረ ስብከት እስከ ዐረፍተ ዘመናቸው ድረስ እንዲቀጥሉ ለማግባባት የነበረ ሲሆን
ምእመናን በቦታው ባለመገኘት ተቃውሟቸውን ገልጸዋል፡፡
ጥቅምት ሲኖዶስ ይጀመር እንጅ ወደ ቅዱስ ሲኖዶስ
ማመልከታችን የማይቀር ነው፡፡ መቼ እንዴት ማን ይሄዳል የሚለውን ነገር ግን ለእናንተ አልናገርም ከፈለጋችሁ እናንተም ተደራጅታችሁ
አዲስ አበባ እንገናኛለን፡፡ መጠየቅ ያለብንን ጉዳይ መጠየቅ ይኖርብናል፡፡ ደግሞ ይህንን ሰምተው እነ አባ እንባቆም እንቅልፍ እንዳያጡ
ነገ ጀምረው አዲስ አበባ ነው የሚገኙት እኮ ለነገሩ አብረውም ሊሰበሰቡ ይችላሉ፡፡ ለማንኛውም እስኪ በምረቃው ወቅት አባ ማርቆስ
ምን ተናገሩ ወደሚለው እንሂድ ለማንኛውም እናንተ ግን ሙሉውን ቪዲዮ ተመልከቱት እኔ ዋና ዋና ነጥቦችን ብቻ ነው የምጠቁም፡፡
1.
እኔ ትንሹ አገልጋይ ይችን
ጸሪቀ መበለት የሆነች የሥራ ፍሬ ስላበረከትሁ ሁላችሁም አጨብጭቡልኝ በማለት አጨብጫቢዎችን አስጨብጭበዋል፡፡ አሁን ይኼ ትህትና
መሆኑ ነው፡፡ እኔ ግን አይመስለኝም፡፡ 4፡45 ላይ አዳምጧቸውማ ትስቃላችሁ እኮ “በርባናስ” ብለው ሲናገሩ “በርናባስ” ለማለት
መሆኑ ነው አይይይ፡፡
2.
ጨሞጋ ላይ ፈለገ አርዝ ካርታ እና ፕላን አስወጣንበት ያሉት የቦታ ስፋት አዳምጡ 8፡48 ላይ አድምጧቸው
96 ሺ ካሬ ሜትር ነው አሉ ስፋቱ ትናንት በላኩላችሁ ቪዲዮ ሥራ አስኪጁ 11፡01 ላይ ሲናገሩ 64 ሺ 5 መቶ ካሬ ሜትር ስፋት
ካርታ እና ፕላን አሰራን ይላሉ፡፡ አባ ማርቆስ ሥራ አስኪጃቸው አባ እንባቆም ከተናገሩት ስፋት 31 ሺ 5 መቶ ካሬ ሜትር ልዩነት
አለ፡፡ ታዲያ ይህ ልዩነት ከየት መጣ ውሸት መሆኑን በዚህ አትረዱም ታዲያ፡፡ ከላይ ባስቀመጥኩላችሁ ደቂቃዎች ላይ ቪዲዮዎችን እየከፈታችሁ
አዳምጧቸው በእውነት እኔ ስለገረመኝ ነው፡፡ በሰው ዘንድ የውሸት ተቀባይነት ለማግኘት አንድ ሊቀ ጳጳስ 31 500 ካሬ ሜትር ውሸት
እንዴት ሊናገር ይችላል፡፡
3.
10፡35 ጀምረው ስለ ህንጻው
ስያሜ ይናገራሉ፡፡ ሕንጻው ራእየ ቅዱስ ወሰማእት ቴዎፍሎስ ነው አሉና መርጡለ ማርያም ሲጠናቀቅ ደግሞ ራእየ ማትያስ እንለዋለን
ብለዋል፡፡ የዚህኛውስ እስኪ ይሁን የዚያኛው ግን እንዴት ሊሆን ይችላል? መርጡለ ማርያሞች ይህን ጉድ ሰምታችኋል ግን? ይህ የሀገረ
ስብከቱ ህንጻ ሁለገብ ህንጻ ስለሆነ የህንጻ ስም ሊስፈልገው ይችላል፡፡ ራእየ ቴዎፍሎስ መባሉም ትክክለኛ ስያሜ ነው፡፡ የቅዱስ
ወሰማእት አቡነ ቴዎፍሎስ መታሰቢያ በጎጃም መኖሩ ይበል የሚያሰኝ ነው፡፡ የመርጡለ ማርያሙ ህንጻ ግን ሁለገብ ህንጻ ሳይሆን ቤተክርስቲያን
ነው፡፡ ታዲያ ቤተክርስቲያኑን “ርእሰ ርኡሳን መርጡለ ማርያም” ገዳም” ተብሎ ይጠራል እንጅ “ራእየ ማትያስ” ቤተክርስቲያን ሊባል ይችላ እንዴ? መርጡለ ማርያሞች የግራኝ
እመቤትን ስም በአባ ማትያስ ስም ሊቀይሩላችሁ ነው አባ ማርቆስ፡፡ ቅርሱን ዘርፈው ጨረሱ በህንጻው ግንባታ ሰበብ ከውጭ አገር ድረስ
ገንዘብ እየለመኑ ለራሳቸው አደረጉ ታዲያ ሰያሜውን ደግሞ ራእየ ማትያስ የሚሉት ምን ሰለሆኑ ነው? መርጡለ ማርያሞች አሁን አሁን
እኮ ነቅታችኋል ይመስለኛል በፊት አካባቢ ነበር ትንሽ መምታታቶች የነበሩት አሁንማ ለይቶላቸዋል እኮ፡፡ ራእየ ማትያስ ብለው አንዱን
ቤተክርስቲያን ሊሰይሙላችሁ እኮ ነው መወዳጃ ሊደርጉት ነው የተነሡ፡፡
4.
13፡18 ክቡር ሥራ አስኪያጁን
አባ ዕንባቆም ነገ የቅዱስነትዎ ልጅ ይሆናል ተብለው ተሚካሽተዋል፡፡ መቼ ይበላሉ መቼ ይተኛሉ እያልሁ አስባለሁ ደማቸውን እስከማፍሰስ
ደርሰዋል ለዚህ ህንጻ አሉላቸው፡፡ እያወቅን ለምን እንሸዋወዳለን አባታችን፡፡ አባ እንባቆም እኮ ደማቸውን ያፈሰሱ እርስዎን በዚህ
ሀገረ ስብከት እንዲቆዩ ለማግባባት ወደ ክልል ሲሄዱ ከመኪና ጋራ ተጋጭተው ነው፡፡ አሁን በቅርቡ ደግሞ የት እንደሚሄዱ ባላውቅም
ከጢቅ አለፍ ብለው ነው ከመኪና ጋር ተጋጭተው ደማቸው የፈሰሰው፡፡ ህንጻው ሲሰራ ብሎኬት አልወደቀባቸው ህንጻ አልተደረመሰባቸው
ምን ሆነው ነው ደማቸው የፈሰሰው ይህ በእውነቱ ሰውን ያለአቅሙ መቆለል ይመስለኛል፡፡
5.
ዕቅድ ብለው ያስቀመጡት ጉዳይ
ዕድሜን ለማራዘም የተጠቀሙበት ዕቅድ ነው፡፡ ብቸና ላይ የመልአከ ብርሃን አድማሱ ጀንበሬን እና የአለቃ አያሌው ታምሩን መታሰቢያ
እንገነባለን ብለዋል፡፡ መልአከ ብርሃንን በተለይ ህዝቡ አያውቅም አሉ፡፡ እኛስ እናውቃቸዋለን በመጽሐፋቸው ተምረናል የማያውቃቸው
ቅባቱ ማኅበረሰብ ብቻ ነው፡፡ በግድ አላውቅም ብሎ ማት ነው እንጅ መልስ ስለመለሱላቸው ያውቋቸዋል፡፡ ባሶ ሊበን ላይ ታሪካቸው
ተዳፍኖ የቀረ መጋቤ ብሉይ ሰይፈ ሥላሴ የሚባሉ አሉ መታሰቢያ ይሠራላቸዋል፡፡ ሞጣ ላይም ገብረ ሥለሴ አንጋፋው መታሰቢያ ይሠራላቸዋል
ብለዋል፡፡ ይህ ሁሉ ዕድሜያቸውን ያራዘሙ ስለመሰላቸው እንጅ የሚሠሩ ሆነው አይደለም፡፡ ቢሠሩ እንኳ የሚሠራቸው ሕዝቡ ነው እንጅ
እርሳቸው አይደሉም፡፡
6.
15፡15 ጀምረው አሜሪካ ከቅዱስ
ፓትርያርኩ ጋር እንተዋወቃለን ይላሉ፡፡ 15፡30 ላይ ሰው አባ ከተባለ ያው ነው ጳጳስ ነው ማለታቸው ነው፡፡ ምንኩስና እና ጵጵስናን
አንድ ሲያደርጉ ትሰማላችሁ፡፡ አረ ስንቱ ኡፍፍፍፍ!!!
7.
ምሥራቅ ጎጃም ላይ እንዲህ
ያለ ህንጻ ይቆማል ብሎ በህልምም የሚስብ የለም ነበር ያሉት 7፡12 ላይ የተናገሯት ነገር በጣም ታሳዝናለች፡፡ ምሥራቅ ጎጃም ከዚህ
የበለጠ ህንጻ አልገነባም እንዴ አብማን አታዩም ገዳመ አስቄጥስን አታዩም በጣም ያሳዝናል፡፡ ራስን ሰማይ ለመስቀል ሲሉ ከስር ያለውን
ምእመን ሥራ ማበላሸት ደስ አይልም፡፡
እናንተ በሙሉ አዳምጡት፡፡ የምረቃውን መርኃ ግብር
በተመለከተ በዚሁ እፈጽማለሁ፡፡ በቀጣይ የአቡነ ማርቆስን በምሥጢር የተቀረጸ መረጃ እለቅላችኋለሁ፡፡ የቅዱስ ማርቆስ ሰንበት ትምህርት
ቤትንም አልረሳሁትም፡፡ አቡነ ማርቆስ ጠባቸው ከምእመናን ጋራ ብቻ አይደለም ከዞኑ አስተዳድር ጋራ ከማኅበረ ቅዱሳን ጋራ ከሰንበት
ትምህርት ቤቶች ጋራ ነው ከሁሉም ጋር ነው፡፡
በውስጥ መስመር መረጃዎችን የምትልኩልኝን ሁሉ
በፈጣሪ ስም ከልብ አመሰግናለሁ፡፡ በነገራችን ላይ መረጃ ሳይኖራችሁ በውስጥ መስመር እየመጣችሁ “ሃይ” ስትሉ የምትውሉ ቦዘኔዎች
ምንም ዓይነት ምላሽ አትጠብቁ ሥራ ፈት መሰልኳችሁ እንዴ? መረጃ ካላችሁ ብቻ በውስጥ መስመር አግኙኝ ከሌላችሁ አታድርቁኝ፡፡ በርካታ
መረጃዎች እየጎረፉልን ነው በቀን በቀን እየተቆጠበ ይለቀቃል፡፡
ዘመነ ማርቆስን ለቤተክርቲያናችን እናድርገው፡፡